ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 40:5-11 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

5. እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፤አንተ ያደረግኸው ድንቅ ነገር ብዙ ነው፤ለእኛ ያቀድኸውን፣ሊዘረዝርልህ የሚችል ማንም የለም፤ላውራው ልናገረው ብል፣ስፍር ቍጥር አይኖረውም።

6. መሥዋዕትንና ቊርባንን አልፈለግህም፤ጆሮቼን ግን ከፈትህ፤የሚቃጠል መሥዋዕትን፣የኀጢአትንም መሥዋዕት አልሻህም።

7. እኔም እንዲህ አልሁ፤ “እነሆ፤ መጥቻለሁ፤ስለ እኔ በመጽሐፍ ተጽፎአል፤

8. አምላኬ ሆይ፤ ፈቃድህን ላደርግ እሻለሁ፤ሕግህም በልቤ ውስጥ አለ።”

9. በታላቅ ጉባኤ ውስጥ ጽድቅን አበሠርሁ፤ እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ እንደምታውቀው፣ከንፈሮቼን አልገጠምሁም።

10. ጽድቅህን በልቤ አልሸሸግሁም፤ታማኝነትህንና ማዳንህን እናገራለሁ፤ምሕረትህንና እውነትህን፣ከታላቅ ጉባኤ አልደበቅሁም።

11. እግዚአብሔር ሆይ፤ ምሕረትህን አትንፈገኝ፤ቸርነትህና እውነትህ ዘወትር ይጠብቁኝ፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 40