ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 22:28-31 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

28. መንግሥት የእግዚአብሔር ናትና፤ሕዝቦችንም የሚገዛ እርሱ ነው።

29. የምድር ከበርቴዎች ይበላሉ፤ይሰግዱለታልም፤ነፍሱን በሕይወት ማቆየት የማይችለው፣ ወደ ዐፈር፣ተመላሽ የሆነው ሁሉ በፊቱ ይንበረከካል።

30. የኋለኛው ትውልድ ያገለግለዋል፤ለመጪው ትውልድ ስለ ጌታ ይነገረዋል።

31. ገና ላልተወለደ ሕዝብ፣ጽድቁን ይነግራሉ፤እርሱ ይህን አድርጎአልና።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 22