ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 136:1-12 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

2. የአማልክትን አምላክ አመስግኑ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

3. የጌቶችን ጌታ አመሰግኑ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

4. እርሱ ብቻውን ታላላቅ ታምራትን የሚያደርግ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤

5. ሰማያትን በብልኀት የሠራ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤

6. ምድርን በውሃ ላይ የዘረጋ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

7. ታላላቅ ብርሃናትን የሠራ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤

8. ፀሓይ በቀን እንዲሠለጥን ያደረገ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤

9. ጨረቃና ከዋክብት በሌሊት እንዲሠለጥኑ ያደረገ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤

10. የግብፅን በኵር የመታ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤

11. እስራኤልን ከመካከላቸው ያወጣ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤

12. በኀያል እጅና በተዘረጋች ክንድ ይህን ያደረገ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 136