ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መክብብ 5:9-17 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

9. ከምድሩ የሚገኘው ትርፍ ለሁሉም ነው፤ ንጉሡም ራሱ የሚጠቀመው ከዕርሻ ነው።

10. ገንዘብን የሚወድ፣ ገንዘብ አይበቃውም፤ብልጽግናም የሚወድ፣ በትርፉ አይረካም፤ይህም ከንቱ ነው።

11. ሀብት በበዛ ቊጥር፣ተጠቃሚውም ይበዛል፤በዐይኑ ብቻ ከማየት በቀርታዲያ፣ ለባለቤቱ ምን ይጠቅመዋል?

12. ጥቂትም ይሁን ብዙ ቢበላ፣የሠራተኛ እንቅልፍ ጣፋጭ ነው፤የሀብታም ሰው ብልጽግና ግንእንቅልፍ ይነሣዋል።

13. ከፀሓይ በታች የሚያሳዝን ክፉ ነገር አየሁ፦ይህም ለባለቤቱ ጒዳት የተከማቸ ሀብት፣

14. ወይም በአንድ መጥፎ አጋጣሚ የጠፋ ብልጽግና ነው፤ልጅ ሲወልድም፣ለእርሱ የሚያስቀርለት ምንም ነገር አይኖርም።

15. ሰው ከእናቱ ማሕፀን ዕራቊቱን ይወለዳል፤እንደ መጣው እንዲሁ ይመለሳል።ከለፋበትም ነገር፣አንድም እንኳ በእጁ ይዞ ሊሄድ አይችልም።

16. ይህ ደግሞ እጅግ ክፉ ነገር ነው፤ሰው እንደ መጣ እንዲሁ ይሄዳል፤የሚደክመው ለነፋስ ስለ ሆነ፣ትርፉ ምንድ ነው?

17. በብዙ ጭንቀት፣ መከራና ብስጭት፣ዘመኑን ሁሉ በጨለማ ውስጥ ይበላል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መክብብ 5