ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሕዝቅኤል 7:2-8 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

2. “አንተ የሰው ልጅ ሆይ፤ ጌታ እግዚአብሔር ለእስራኤል ምድር እንዲህ ይላል፤ ‘ፍጻሜ! በአራቱም የምድሪቱ ማእዘን ፍጻሜ መጥቶአል።

3. አሁንም መጨረሻሽ ደርሶአል፤ ቍጣዬን በአንቺ ላይ አፈሳለሁ፤ እንደ አካሄድሽ እፈርድብሻለሁ፤ ስለ ጸያፍ ተግባርሽ ሁሉ ተገቢውን ቅጣት እከፍልሻለሁ።

4. በርኅራኄ ዐይን አልመለከትሽም፤ ምሕረትም አላደርግልሽም፤ ስለ አካሄድሽና በመካከልሽ ስላለው ጸያፍ ተግባር ተገቢውን ቅጣት እከፍልሻለሁ፤ በዚያ ጊዜ እኔ እግዚአብሔር እንደሆንሁ ታውቃላችሁ።”

5. “ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘መዓት! ተሰምቶ የማይታወቅ መዓት ይመጣል።

6. ፍጻሜ መጥቶአል! ፍጻሜ መጥቶአል! በአንቺ ላይ ተነሣሥቶአል፤ እነሆ፤ ደርሶአል!

7. እናንት በምድሪቱ የምትኖሩ ሆይ፤ የጥፋት ፍርድ መጥቶባችኋል፤ ጊዜው ደርሶአል፤ በተራሮች ላይ እልልታ ሳይሆን ሽብር የሚሰማበት ቀን ቀርቦአል።

8. እነሆ፤ መዓቴን በቅርብ ቀን አፈስብሻለሁ፤ በአንቺ ላይ ቍጣዬን እፈጽምብሻለሁ፤ እንደ አካሄድሽ እፈርድብሻለሁ፤ ስለ ጸያፍ ተግባርሽም ሁሉ ተገቢውን ቅጣት እከፍልሻለሁ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሕዝቅኤል 7