ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሕዝቅኤል 21:28-32 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

28. “አንተ የሰው ልጅ ሆይ! እንዲህ ብለህ ተናገር፤ ‘ስለ አሞናውያንና ስለ ስድባቸው ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ ‘ሰይፍ! ሰይፍ!ሊገድል የተመዘዘ፣ሊያጠፋ የተጠረገ፣እንደ መብረቅ ሊያብረቀርቅ የተወለወለ፤

29. የታለመልህ የሐሰት ራእይ፣የተነገረልህ የውሸት ሟርት ቢኖርም፣የግፍ ጽዋቸው በሞላ፣ቀናቸው በደረሰ፣መታረድ በሚገባቸው ክፉዎች፣አንገት ላይ ይሆናል።

30. ሰይፉን ወደ ሰገባው መልሰው፤በተፈጠርህበት ምድር፣በተወለድህበትም አገር፣በዚያ እፈርድብሃለሁ።

31. መዓቴን በላይህ አፈሳለሁ፤የቍጣዬንም እሳት አነድብሃለሁ፣በጥፋት ለተካኑ፣ለጨካኞች ሰዎች አሳልፌ እሰጥሃለሁ።

32. ለእሳት ማገዶ ትሆናለህ፣ደምህ በምድርህ ይፈሳል፣ከእንግዲህ መታሰቢያ አይኖርህም፤እኔ እግዚአብሔር ተናግሬአለሁና።’ ”

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሕዝቅኤል 21