ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሕዝቅኤል 21:25-32 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

25. “ ‘አንተ የግፍ ጽዋህ የሞላ፣ የምትቀጣበት ቀን የደረሰ፣ ርኩስና ክፉ የእስራኤል መስፍን ሆይ፤

26. ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “ጥምጥምህን አውልቅ፤ ዘውድህን ጣል፤ እንደ ከዚህ በፊቱ አይሆንም፤ ዝቅ ያለው ከፍ ይላል፤ ከፍ ያለውም ዝቅ ይላል።

27. ባድማ! ባድማ! ባድማ አደርጋታለሁ፤ የሚገባው ባለ መብት እስከሚመጣ ድረስ እንደ ቀድሞው አትሆንም፤ ለእርሱም ደግሞ እሰጣታለሁ።” ’

28. “አንተ የሰው ልጅ ሆይ! እንዲህ ብለህ ተናገር፤ ‘ስለ አሞናውያንና ስለ ስድባቸው ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ ‘ሰይፍ! ሰይፍ!ሊገድል የተመዘዘ፣ሊያጠፋ የተጠረገ፣እንደ መብረቅ ሊያብረቀርቅ የተወለወለ፤

29. የታለመልህ የሐሰት ራእይ፣የተነገረልህ የውሸት ሟርት ቢኖርም፣የግፍ ጽዋቸው በሞላ፣ቀናቸው በደረሰ፣መታረድ በሚገባቸው ክፉዎች፣አንገት ላይ ይሆናል።

30. ሰይፉን ወደ ሰገባው መልሰው፤በተፈጠርህበት ምድር፣በተወለድህበትም አገር፣በዚያ እፈርድብሃለሁ።

31. መዓቴን በላይህ አፈሳለሁ፤የቍጣዬንም እሳት አነድብሃለሁ፣በጥፋት ለተካኑ፣ለጨካኞች ሰዎች አሳልፌ እሰጥሃለሁ።

32. ለእሳት ማገዶ ትሆናለህ፣ደምህ በምድርህ ይፈሳል፣ከእንግዲህ መታሰቢያ አይኖርህም፤እኔ እግዚአብሔር ተናግሬአለሁና።’ ”

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሕዝቅኤል 21