ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሆሴዕ 12:1-9 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ኤፍሬም የነፋስ እረኛ ነው፤ቀኑን ሙሉ የምሥራቅን ነፋስ ይከተላል፤ሐሰትንና ዐመፅን ያበዛል።ከአሦር ጋር ቃል ኪዳን ያደርጋል፤የወይራ ዘይትንም ወደ ግብፅ ይልካል።

2. እግዚአብሔር በይሁዳ ላይ የሚያቀርበው ክስ አለው፤ያዕቆብን እንደ መንገዱ ይቀጣዋል፤እንደ ሥራውም ይከፍለዋል።

3. በማሕፀን ሳለ የወንድሙን ተረከዝ ያዘ፤ሙሉ ሰውም ሲሆን ከአምላክ ጋር ታገለ።

4. ከመልአኩም ጋር ታገለ፤ አሸነፈውም፤በፊቱ ሞገስን ለማግኘት አልቅሶ ለመነው፣እርሱንም በቤቴል አገኘው፤በዚያም ከእርሱ ጋር ተነጋገረ፤

5. እርሱም ሁሉን የሚገዛ አምላክ እግዚአብሔር፣የሚታወቅበት ስሙም እግዚአብሔር ነው።

6. ስለዚህ ወደ አምላክህ ተመለስ፤ፍቅርንና ፍትሕን ጠብቅ፤ዘወትርም በአምላክህ ታመን።

7. ነጋዴው በሐሰተኛ ሚዛን ይሸጣል፤ማጭበርበርንም ይወዳል።

8. ኤፍሬም እንዲህ እያለ ይታበያል፤“እኔ ባለጠጋ ነኝ፤ ሀብታምም ሆኛለሁ፤ይህ ሁሉ ሀብት እያለኝ፣ምንም ዐይነት በደል ወይም ኀጢአት አያገኙብኝም።”

9. “ከግብፅ ምድር ያወጣኋችሁ፣ አምላካችሁ እግዚአብሔር እኔ ነኝ፤በዓመት በዓላችሁ ቀን ታደርጉ እንደ ነበረው ሁሉ፣እንደ ገና በድንኳኖች እንድትቀመጡአደርጋችኋለሁ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሆሴዕ 12