ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

2 ነገሥት 19:29-37 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

29. “ሕዝቅያስ ሆይ፤ ምልክቱ ይህ ነው፤“በዚህ ዓመት በገዛ እጁ የበቀለውን፣በሚመጣው ዓመት ደግሞ የገቦውን እህል ትበላላችሁ፤በሦስተኛው ዓመት ግን ትዘራላችሁ፤ ታጭዳላችሁ፤ወይንም ትተክላላችሁ፤ ፍሬውንም ትበላላችሁ።

30. አሁንም ከዳዊት ቤት የተረፉት፣ሥራቸውን ወደ ታች ይሰዳሉ፤ ወደ ላይም ፍሬ ያፈራሉ።

31. ከኢየሩሳሌም በሕይወት የተረፉት፣ከጽዮን ተራራም ከሞት ያመለጡት ይወጣሉና። የእግዚአብሔር ቅናት ይህን ታደርጋለች።

32. “እንግዲህ እግዚአብሔር ስለ አሦር ንጉሥ የሚለው ይህ ነው፤“ወደዚች ከተማ ፈጽሞ አይገባም፤አንዲትም ፍላጻ አይወረውርባትም፤ጋሻ አንግቦ ወደ እርሷ አይቀርብም፤በዐፈርም ቊልል አይከባትም።

33. በመጣበት መንገድ ተመልሶ ይሄዳል፤ተመልሶ ይሄዳታል እንጂ ወደዚች ከተማ ፈጽሞ አይገባም፤ይላል እግዚአብሔር።

34. ስለ ራሴና ስለ ባሪያዬም ስለ ዳዊት ስል፣ይህችን ከተማ አድናት ዘንድ እጋርዳታለሁ።

35. በዚያችም ሌሊት የእግዚአብሔር መልአክ ወጥቶ ከአሦራውያን ሰፈር መቶ ሰማንያ አምስት ሺህ ሰው ገደለ። በማግስቱም ሰዎቹ ሲነቁ ቦታው ሬሳ በሬሳ ሆኖ ተገኘ።

36. የአሦር ንጉሥ ሰናክሬም ከዚያ ተነሥቶ ሄደ፤ ወደ ነነዌም ተመልሶ በዚያ ተቀመጠ።

37. አንድ ቀንም ናሳራክ በተባለው አምላኩ ቤተ ጣዖት ገብቶ በመስገድ ላይ ሳለ፣ አድራሜሌክና ሳራሳር የተባሉ ልጆቹ በሰይፍ ገደሉት፤ ከዚያም አምልጠው ወደ አራራት ሸሹ። ልጁ አስራዶንም በእግሩ ተተክቶ ነገሠ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ 2 ነገሥት 19