ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

2 ሳሙኤል 1:20-27 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

20. “ይህን በጌት አትናገሩ፤በአስቀሎናም መንገዶች አታውጁት፤የፍልስጥኤም ቈነጃጅት አይደሰቱ፤ያልተገረዙት ሴቶች ልጆች እልል አይበሉ።

21. “እናንተ የጊልቦዓ ተራሮች ሆይ፤ጠል አያረስርሳችሁ፤ዝናብም አይውረድባችሁ፤የቍርባን እህል የሚያበቅሉም ዕርሻዎች አይኑራቸው፤በዚያ የኀያሉ ሰው ጋሻ ረክሶአልና፤ የሳኦል ጋሻ ከእንግዲህ በዘይት አይወለወልም።

22. ከሞቱት ሰዎች ደም፣ከኀያላኑም ሥብ፣የዮናታን ቀስት ተመልሳ አልመጣችም፤የሳኦልም ሰይፍ በከንቱ አልተመለሰችም።

23. “ሳኦልና ዮናታን በሕይወት እያሉ፣የሚዋደዱና የሚስማሙ ነበሩ፤ሲሞቱም አልተለያዩም፤ከንስርም ይልቅ ፈጣኖች፣ከአንበሳም ይልቅ ብርቱዎች ነበሩ።

24. “እናንት የእስራኤል ቈነጃጅት ሆይ፤ሐምራዊ ቀሚስና ቀጭን ፈትል ላለበሳችሁ፣ልብሶቻችሁንም በወርቀ ዘቦ ላስጌጠላችሁ፣ለሳኦል አልቅሱለት።

25. “ኀያላን እንዴት እንዲህ በጦርነት ወደቁ!ዮናታን በኰረብቶችህ ላይ ተወግቶ ሞቶአል።

26. ወንድሜ ዮናታን ሆይ፤ እኔ ስለ አንተ አዘንሁ፤አንተ ለእኔ እጅግ ውድ ነበርህ፤ፍቅርህ ለእኔ ድንቅ ነበረ፤ከሴት ፍቅርም ይልቅ ግሩም ነበር።

27. “ኀያላኑ እንዴት ወደቁ!የጦር መሣሪያዎቹስ እንዴት ከንቱ ይሁኑ!”

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ 2 ሳሙኤል 1