ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

1 ዜና መዋዕል 7:7-19 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

7. የቤላ ወንዶች ልጆች፤ኤሴቦን፣ ኦዚ፣ ዑዝኤል፣ ኢያሪሙት፣ ዒሪ፤ ባጠቃላይ አምስት ሲሆኑ፣ የቤተ ሰብ አለቆች ናቸው፤ በትውልድ ሐረግ መዝገባቸው ሃያ ሁለት ሺህ ሠላሳ አራት ተዋጊ ሰዎች ተመዝግበዋል።

8. የቤኬር ወንዶች ልጆች፤ዝሚራ፣ ኢዮአስ፣ አልዓዛር፣ ኤልዮዔናይ፣ ዖምሪ፣ ኢያሪሙት፣ አብያ፣ ዓናቶት፣ ዓሌሜት፤ እነዚህ ሁሉ የቤኬር ልጆች ነበሩ።

9. በትውልድ ሐረግ መዝገባቸውም ውስጥ የየቤተ ሰባቸው አለቆችና ሃያ ሺህ ሁለት መቶ ተዋጊዎች ተመዝግበዋል።

10. የይዲኤል ልጅ፤ቢልሐን።የቢልሐን ወንዶች ልጆች፤የዑስ፣ ብንያም፣ ኤሁድ፣ ክንዓና፣ ዜታን፣ ተርሴስ፣ አኪሳኦር፤

11. እነዚህ ሁሉ የይዲኤል ልጆች የየቤተ ሰቡ አለቆች ነበሩ፤ እነርሱም ለውጊያ ብቁ የሆኑ ዐሥራ ሰባት ሺህ ተዋጊዎች ነበሯቸው።

12. ሳፈንና ሑፊም የዒር ዘሮች ሲሆኑ፣ ሑሺም ደግሞ የአሔር ዘር ነው።

13. የንፍታሌም ወንዶች ልጆች፤ያሕጽሔል፣ ጉኒ፣ ዬጽር፣ ሺሌም፤ እነዚህ የባላ ዘሮች ናቸው።

14. የምናሴ ዘሮች፤ሶርያዊት ቁባቱ የወለደችለት ልጁ አሥርኤል ነው። እርሷም የገለዓድን አባት ማኪርን የወለደች ናት፤

15. ማኪርም ከሑፊምና ከሳፊም ወገኖች ሚስት አገባ። እኅቱም መዓካ ትባል ነበር።ሌላው ዘሩ ሰለጰዓድ ሲሆን፣ እርሱም ሴቶች ልጆች ብቻ ነበሩት።

16. የሚኪር ሚስት መዓካ ወንድ ልጅ ወለደች፤ ስሙንም ፋሬስ አለችው። የወንድሙም ስም ሱሮስ ይባላል፤ ወንዶች ልጆቹም ኡላምና ራቄም ነበሩ።

17. የኡላም ወንድ ልጅ፤ባዳን፤እነዚህ የምናሴ ልጅ፣ የማኪር ልጅ፣ የገለዓድ ወንዶች ልጆች ናቸው፤

18. እኅቱ መለኬት ኢሱድን፣ አቢዔዝርንና መሕላን ወለደች።

19. የሸሚዳ ወንዶች ልጆች ደግሞ እነዚህ ነበሩ፤አሒያን፣ ሴኬም፣ ሊቅሒ፣ አኒዓም።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ 1 ዜና መዋዕል 7