ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

1 ዜና መዋዕል 4:27-35 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

27. ሰሜኢ ዐሥራ ስድስት ወንዶችና ስድስት ሴቶች ልጆች ነበሩት፤ ወንድሞቹ ግን ብዙ ልጆች አልነበሯቸውም፤ ስለዚህ ጐሣቸው በሙሉ እንደ ይሁዳ ሕዝብ ብዙ አልነበረም።

28. የኖሩባቸውም ቦታዎች እነዚህ ናቸው፤ ቤርሳቤህ፣ ሞላደ፣ ሐጻርሹዓል፣

29. ቢልሃ፣ ዔጼም፣ ቶላድ፣

30. ቤቱኤል፣ ሔርማ፣ ጺቅላግ፣

31. ቤትማርካቦት፣ ሐጸርሱሲም፣ ቤት ቢሪ፣ ሽዓራይም፤ እስከ ዳዊት ዘመነ መንግሥት ድረስ የኖሩት በእነዚህ ከተሞች ነው።

32. በአካባቢያቸው የሚገኙት መንደሮች ደግሞ ኤጣም፣ ዓይን፣ ሬሞን፣ ቶኬን፣ ዓሻን የተባሉ አምስት ከተሞች ናቸው፤

33. በእነዚህም ከተሞች ዙሪያ እስከ በኣል የሚዘልቁ መንደሮች ነበሩ፤ መኖሪያቸው በዚሁ ሲሆን፣ የትውልድ መዝገብም አላቸው።

34. ሞሾባብ፣ የምሌክ፣ የአሜስያስ ልጅ ኢዮስያስ፣

35. ኢዮኤል፣ የዮሺብያ ልጅ፣ የሠራያ ልጅ፣ የዓሢኤል ልጅ ኢዩ

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ 1 ዜና መዋዕል 4