ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

1 ዜና መዋዕል 4:23-31 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

23. ሰዎቹ በነጣዒምና በጋዴራ የሚቀመጡ ሸክላ ሠሪዎች ነበሩ፤ በዚያም በመቀመጥ ለንጉሡ ሸክላ ይሠሩ ነበር።

24. የስምዖን ዘሮች፤ነሙኤል፣ ያሚን፣ ያሪን፣ ዛራ፣ ሳኡል፤

25. ሰሎም የሳኡል ልጅ ነው፤ መብሳም የሰሎም ልጅ ነው፤ማስማዕ ደግሞ የመብሳም ልጅ ነው።

26. የማስማዕ ዘሮችልጁ ሃሙኤል፣ ልጁ ዘኩር፣ ልጁ ሰሜኢ።

27. ሰሜኢ ዐሥራ ስድስት ወንዶችና ስድስት ሴቶች ልጆች ነበሩት፤ ወንድሞቹ ግን ብዙ ልጆች አልነበሯቸውም፤ ስለዚህ ጐሣቸው በሙሉ እንደ ይሁዳ ሕዝብ ብዙ አልነበረም።

28. የኖሩባቸውም ቦታዎች እነዚህ ናቸው፤ ቤርሳቤህ፣ ሞላደ፣ ሐጻርሹዓል፣

29. ቢልሃ፣ ዔጼም፣ ቶላድ፣

30. ቤቱኤል፣ ሔርማ፣ ጺቅላግ፣

31. ቤትማርካቦት፣ ሐጸርሱሲም፣ ቤት ቢሪ፣ ሽዓራይም፤ እስከ ዳዊት ዘመነ መንግሥት ድረስ የኖሩት በእነዚህ ከተሞች ነው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ 1 ዜና መዋዕል 4