ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

1 ዜና መዋዕል 26:1-9 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. የቤተ መቅደሱ በር ጠባቂዎች አመዳደብ፤ከቆሬያውያን ወገን፤ ከአሳፍ ወንዶች ልጆች አንዱ የሆነው የቆሬ ወንድ ልጅ ሜሱላም።

2. ሜሱላም ወንዶች ልጆች ነበሩት፤የመጀመሪያው ዘካሪያስ፣ሁለተኛው ይዲኤል፣ሦስተኛው ዮዛባት፣አራተኛው የትኒኤል፣

3. አምስተኛው ኤላም፣ስድስተኛው ይሆሐናን፣ሰባተኛው ኤሊሆዔናይ።

4. ዖቤድኤዶምም እንደዚሁ ወንዶችልጆች ነበሩት፤የመጀመሪያው ሸማያ፣ሁለተኛው ዮዛባት፣ሦስተኛው ኢዮአስ፣አራተኛው ሣካር፣አምስተኛው ናትናኤል፣

5. ስድስተኛው ዓሚኤል፣ሰባተኛው ይሳኮር፣ስምንተኛው ፒላቲ፤እግዚአብሔር ዖቤድኤዶምን ባርኮታልና።

6. እንዲሁም ልጁ ሸማያ ወንዶች ልጆች ነበሩት፤ እነርሱም በቂ ችሎታ ስለ ነበራቸው የአባታቸው ቤት መሪዎች ሆነው ነበር።

7. የሽማያ ወንዶች ልጆች፤ ዖትኒ፣ ራፋኤል፣ ዖቤድ፣ ኤልዛባድ፤ ዘመዶቹ ኤሊሁና ሰማክያም እንደዚሁ በቂ ችሎታ ነበራቸው።

8. እነዚህ ሁሉ የዖቤድኤዶም ዘሮች ሲሆኑ፣ እነርሱም ሆኑ ወንዶች ልጆቻቸውና ቤተ ዘመዶቻቸው ሥራውን ለመሥራት በቂ ችሎታ ነበራቸው። የዖቤድኤዶም ዘሮች ባጠቃላይ ሥልሳ ሁለት ነበሩ።

9. ሜሱላም በቂ ችሎታ ያላቸው ወንዶች ልጆችና ቤተ ዘመዶች ነበሩት፤ ቊጥራቸውም ባጠቃላይ ዐሥራ ስምንት ነበረ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ 1 ዜና መዋዕል 26