ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

1 ዜና መዋዕል 2:29-40 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

29. የአቢሱር ሚስት አቢካኢል ትባላለች፤ እርሷም አሕባንንና ሞሊድ የተባሉ ልጆች ወለደችለት።

30. የናባድ ወንዶች ልጆች፤ሴሌድ፣ አፋይም፤ ሴሌድ ወንድ ልጅ ሳይወልድ ሞተ።

31. የአፋይም ወንድ ልጅ፤ይሽዒ። ይሽዒም ሶሳን ወለደ።ሶሳን አሕላይን ወለደ።

32. የሸማይ ወንድም የያዳ ወንዶች ልጆች፤ ዬቴር፣ ዮናታን፤ ዬቴርም ልጅ ሳይወልድ ሞተ።

33. የዮናታን ወንዶች ልጆች፤ፌሌት፣ ዛዛ።እነዚህ የይረሕምኤል ዘሮች ነበሩ።

34. ሶሳን ሴቶች ልጆች እንጂ ወንዶች ልጆች አልነበሩትም።እርሱም ኢዮሄል የተባለ ግብፃዊ አገልጋይ ነበረው።

35. ሶሳን ልጁን ለአገልጋዩ ለኢዮሄል ሚስት ትሆነው ዘንድ ሰጠው፤ እርሷም ዓታይ የተባለ ወንድ ልጅ ወለደችለት።

36. ዓታይ ናታንን ወለደ፤ናታንም ዛባድን ወለደ፤

37. ዛባድ ኤፍላልን ወለደ፤ኤፍላል ዖቤድን ወለደ፤

38. ዖቤድ ኢዩን ወለደ፤ኢዩ ዓዛርያስን ወለደ፤

39. ዓዛርያስ ኬሌስን ወለደ፤ኬሌስ ኤልዓሣን ወለደ፤

40. ኤልዓሣ ሲስማይን ወለደ፤ሲስማይ ሰሎምን ወለደ፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ 1 ዜና መዋዕል 2