ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

1 ዜና መዋዕል 16:6-13 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

6. እንዲሁም ካህናቱ በናያስና የሕዚኤል ዘወትር በእግዚአብሔር የኪዳኑ ታቦት ፊት መለከት እንዲነፉ ተመደቡ።

7. በዚያም ቀን ዳዊት በመጀመሪያ ለአሳፍና ለሥራ ጓደኞቹ ይህን የእግዚአብሔር ምስጋና መዝሙር ሰጠ፤

8. ለእግዚአብሔር ምስጋና አቅርቡ፤ ስሙንም ጥሩ፤ለአሕዛብ ያደረገውን ሁሉ ንገሩ፤

9. ዘምሩለት፤ ውዳሴም አቅርቡለት፤ድንቅ ሥራውን ሁሉ ንገሩ፤

10. በቅዱስ ስሙ ተጓደዱ፤ እግዚአብሔርን የሚፈልጉ ሁሉ፣ ልባቸው ሐሤት ያድርግ።

11. ወደ እግዚአብሔርና ወደ ኀይሉ ተመልከቱ፤ዘወትር ፊቱን ፈልጉ።

12. ያደረጋቸውን ድንቅ ሥራዎች፣ታምራቱንና የሰጠውንም ፍርድ አስታውሱ፤

13. እናንተ የባሪያው የእስራኤል ዘሮች፣እናንተ የተመረጣችሁ የያዕቆብ ልጆች።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ 1 ዜና መዋዕል 16