ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

1 ነገሥት 4:8-22 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

8. ስማቸውም እንደሚከተለው ነው፤ቤንሑር፣ በኰረብታማው በኤፍሬምምድር፤

9. ቤንጼቄር፣ በማቃጽ፣ በሻዓልቢም፣በቤትሳሜስ፣ በኤሎንቤትሐናን፤

10. ቤንሔሴድ፣ በአሩቦት ውስጥየሚገኙት ሰኰትና የኦፌር አገርበሙሉ የእርሱ ነበር፤

11. ቤን አሚናዳብ፤ በናፎትረ ዶር፣እርሱም የሰሎሞንን ልጅ ጣፈትንአግብቶ የነበረ ነው፤

12. የአሒሉድ ልጅ በዓና፣ በታዕናክናበመጊዶ እንዲሁም ከጻርታን ቀጥሎቍልቍል እስከ ኢይዝራኤል ባለውበቤትሳን ሁሉ፣ ከዚያም ዮቅምዓምንተሻግሮ እስከ አቤልምሖላና ድረስ፣

13. ቤንጌበር፣ በገለዓድ ራሞት ከተማእዚያው ገለዓድ ውስጥ የምናሴልጅ የኢያዕር መንደሮች፣ በባሳንምየአርጎብ አውራጃ እንዲሁም በሮቻቸው የናስ መወርወሪያ በሆኑ ሥልሳባለ ቅጥር ታላላቅ ከተሞች፤

14. የዒዶ ልጅ አሒናዳብ፤ በማሃናይም፣

15. አኪማአስ በንፍታሌም፣ እርሱምየሰሎሞንን ልጅ ባስማትን አግብቶየነበረ ነው፤

16. የኩሲ ልጅ በዓና፤ በአሴርና በበዓሎት፣

17. የፋሩዋ ልጅ ኢዮሣፍጥ በይሳኮር፣

18. የኤላ ልጅ ሳሚ በብንያም፣

19. የኡሪ ልጅ ጌበር፤በአሞራውያን ንጉሥ በሴዎን ምድር፣በባሳን ንጉሥ በዐግ አገር፣ እርሱምየአውራጃው ብቸኛ ገዥ ነበር።

20. የይሁዳና የእስራኤል ሕዝቦች ብዛታቸው እንደ ባሕር ዳር አሸዋ ሆነ፤ ይበሉ፣ ይጠጡና ይደሰቱም ነበር።

21. ሰሎሞንም ከወንዙ አንሥቶ እስከ ፍልስጥኤማውያን ምድር፣ ከዚያም እስከ ግብፅ ዳርቻ ያሉትን መንግሥታት ሁሉ ገዛ፤ እነዚህም አገሮች ግብር አመጡለት፤ በሕይወት ዘመኑም ሁሉ ተገዙለት።

22. ለሰሎሞን በየቀኑ የሚገባለትም ቀለብ ይህ ነበር፤ ሠላሳ ኮር ማለፊያ ዱቄት፣ ሥልሳ ኮር መናኛ ዱቄት፣

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ 1 ነገሥት 4