7. ነገር ግን፣ እውነት እላችኋለሁ፤ መሄዴ ይበጃችኋል። እኔ ካልሄድሁ አጽናኙ ወደ እናንተ አይመጣም፤ ከሄድሁ ግን እርሱን ወደ እናንተ እልካለሁ፤
8. በሚመጣበትም ጊዜ ዓለምን ስለ ኀጢአት፣ ስለ ጽድቅና ስለ ፍርድ ይወቅሳል።
9. ስለ ኀጢአት ሲባል፣ ሰዎች በእኔ ስለማያምኑ ነው፤
10. ስለ ጽድቅ፣ ወደ አብ ስለምሄድና ከእንግዲህ ስለማታዩኝ ነው፤
11. ስለ ፍርድም፣ የዚህ ዓለም ገዥ ስለ ተፈረደበት ነው።