ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዮሐንስ 11:31-37 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

31. ማርያምን ሲያጽናኑ በቤት ውስጥ የነበሩ አይሁድም፣ ብድግ ብላ መውጣቷን ሲያዩ፣ ወደ መቃብሩ ሄዳ የምታለቅስ መስሎአቸው ተከተሏት።

32. ማርያምም ኢየሱስ ወደነበረበት ቦታ ደርሳ እንዳየችው፣ እግሩ ላይ ተደፍታ፣ “ጌታ ሆይ፤ አንተ እዚህ ብትሆን ኖሮ፣ ወንድሜ ባልሞተ ነበር” አለችው።

33. ኢየሱስም እርሷ ስታለቅስ፣ ተከትለዋትም የመጡት አይሁድም ሲያለቅሱ ባየ ጊዜ መንፈሱ በኀዘን ታውኮ፣

34. “የት ነው ያኖራችሁት?” ሲል ጠየቀ።እነርሱም፣ “ጌታ ሆይ፤ መጥተህ እይ” አሉት።

35. ኢየሱስም እንባውን አፈሰሰ።

36. አይሁድም፣ “እንዴት ይወደው እንደ ነበር አያችሁ” አሉ።

37. ከእነርሱ አንዳንዶቹ ግን፣ “የዐይነ ስውሩን ዐይን የከፈተ፣ ይህም ሰው እንዳይሞት ማድረግ አይችልም ነበር?” አሉ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዮሐንስ 11