7. ስለዚህ እንዲህ ካሉ ጋር አትተባበሩ።
8. ቀድሞ ጨለማ ነበራችሁ፤ አሁን ግን በጌታ ብርሃን ናችሁ። እንደ ብርሃን ልጆች ኑሩ፤
9. የብርሃኑ ፍሬ በበጎነት፣ በጽድቅና በእውነት ሁሉ ዘንድ ነውና።
10. እንዲሁም ጌታን ደስ የሚያሰኘውን ፈልጉ።
11. ፍሬ ከሌለው ከጨለማ ሥራ ጋር ምንም ዐይነት ግንኙነት አይኑራችሁ፤ ይልቁን ግለጡት፤
12. በድብቅ የሚሠሩትን ነገር መናገር ራሱ አሳፋሪ ነውና።
13. ብርሃን የበራበት ነገር ሁሉ ግልጽ ሆኖ ይታያል፤