ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤፌሶን 5:6-20 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

6. ማንም በከንቱ ንግግር አያታላችሁ፤ ምክንያቱም የእግዚአብሔር ቊጣ በማይታዘዙ ልጆች ላይ የሚመጣው በእንደዚህ ዐይነት ነገር ነው።

7. ስለዚህ እንዲህ ካሉ ጋር አትተባበሩ።

8. ቀድሞ ጨለማ ነበራችሁ፤ አሁን ግን በጌታ ብርሃን ናችሁ። እንደ ብርሃን ልጆች ኑሩ፤

9. የብርሃኑ ፍሬ በበጎነት፣ በጽድቅና በእውነት ሁሉ ዘንድ ነውና።

10. እንዲሁም ጌታን ደስ የሚያሰኘውን ፈልጉ።

11. ፍሬ ከሌለው ከጨለማ ሥራ ጋር ምንም ዐይነት ግንኙነት አይኑራችሁ፤ ይልቁን ግለጡት፤

12. በድብቅ የሚሠሩትን ነገር መናገር ራሱ አሳፋሪ ነውና።

13. ብርሃን የበራበት ነገር ሁሉ ግልጽ ሆኖ ይታያል፤

14. ምክንያቱም ሁሉን ነገር እንዲታይ የሚያደርገው ብርሃን ነውና፤ ስለዚህም፣“አንተ የተኛህ ንቃ፤ከሙታን ተነሣ፤ክርስቶስም ያበራልሃል” ተብሎአል።

15. እንግዲህ ጥበብ እንደሌላቸው ሳይሆን እንደ ጥበበኞች እንዴት እንደምትኖሩ ተጠንቀቁ።

16. ቀኖቹ ክፉ ናቸውና ዘመኑን በሚገባ ዋጁ።

17. ስለዚህ ሞኞች አትሁኑ፤ የጌታ ፈቃድ ምን እንደሆነ አስተውሉ እንጂ።

18. በመንፈስ ተሞሉ እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ፤ ይህ ብክነት ነውና።

19. በመዝሙርና በውዳሴ፣ በመንፈሳዊም ዝማሬ እርስ በርሳችሁ ተነጋገሩ፤ በልባችሁ ለጌታ ተቀኙ፤ አዚሙም።

20. በዚህም እግዚአብሔር አብን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ስለ ሁሉ ነገር ሁል ጊዜ አመስግኑ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኤፌሶን 5