ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤፌሶን 5:5-13 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

5. ደግሞም ይህን ዕወቁ፤ ማንም አመንዝራ ወይም ርኩስ ወይም ስግብግብ ይኸውም ጣዖት አምላኪ በክርስቶስና በእግዚአብሔር መንግሥት ርስት የለውም።

6. ማንም በከንቱ ንግግር አያታላችሁ፤ ምክንያቱም የእግዚአብሔር ቊጣ በማይታዘዙ ልጆች ላይ የሚመጣው በእንደዚህ ዐይነት ነገር ነው።

7. ስለዚህ እንዲህ ካሉ ጋር አትተባበሩ።

8. ቀድሞ ጨለማ ነበራችሁ፤ አሁን ግን በጌታ ብርሃን ናችሁ። እንደ ብርሃን ልጆች ኑሩ፤

9. የብርሃኑ ፍሬ በበጎነት፣ በጽድቅና በእውነት ሁሉ ዘንድ ነውና።

10. እንዲሁም ጌታን ደስ የሚያሰኘውን ፈልጉ።

11. ፍሬ ከሌለው ከጨለማ ሥራ ጋር ምንም ዐይነት ግንኙነት አይኑራችሁ፤ ይልቁን ግለጡት፤

12. በድብቅ የሚሠሩትን ነገር መናገር ራሱ አሳፋሪ ነውና።

13. ብርሃን የበራበት ነገር ሁሉ ግልጽ ሆኖ ይታያል፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኤፌሶን 5