ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሮሜ 12:16-21 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

16. እርስ በርሳችሁ በመስማማት ኑሩ። ዝቅተኛ ኑሮ ውስጥ ካሉ ጋር አብራችሁ ለመሆን ፍቀዱ እንጂ አትኵራሩ፤ በራሳችሁም አትመኩ።

17. ለማንም ክፉን በክፉ አትመልሱ፤ በሰው ሁሉ ፊት በጎ የሆነውን ነገር ለማድረግ ትጉ።

18. ቢቻላችሁስ በበኩላችሁ ከሰው ሁሉ ጋር በሰላም ኑሩ።

19. ወዳጆቼ ሆይ፤ ለእግዚአብሔር ቊጣ ፈንታ ስጡ እንጂ አትበቀሉ፤ “በቀል የእኔ ነው፤ እኔ ብድራትን እመልሳለሁ” ይላል ጌታ ተብሎ ተጽፎአልና።

20. ይልቁንስ፣“ጠላትህ ቢራብ አብላው፤ቢጠማም አጠጣው።ይህን በማድረግህም የእሳት ፍም በራሱ ላይ ትከምራለህ።”

21. ክፉን በመልካም አሸንፍ እንጂ በክፉ አትሸነፍ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሮሜ 12