ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ራእይ 7:6-11 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

6. ከአሴር ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺህ፣ከንፍታሌም ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺህ፣ከምናሴ ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺህ፣

7. ከስምዖን ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺህ፣ከሌዊ ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺህ፣ከይሳኮር ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺህ፣

8. ከዛብሎን ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺህ፣ከዮሴፍ ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺህ፣ከብንያም ነገድ ዐሥራ ሁለት ሺህ ታተሙ።

9. ከዚህም በኋላ አየሁ፤ እነሆ፤ በዙፋኑና በበጉ ፊት ማንም ሊቈጥራቸው የማይችል ከሕዝብ፣ ከነገድ፣ ከወገን፣ ከቋንቋም ሁሉ እጅግ ብዙ ሕዝብ ቆመው ነበር፤ እነርሱም ነጭ ልብስ ለብሰው፣ የዘንባባ ዝንጣፊ በእጃቸው ይዘው ነበር።

10. በታላቅ ድምፅም እንዲህ ብለው ጮኹ፤“ማዳን በዙፋኑ ላይ የተቀመጠው፣የአምላካችንና የበጉ ነው።”

11. መላእክቱም ሁሉ በዙፋኑና በሽማግሌዎቹ፣ በአራቱም ሕያዋን ፍጡራን ዙሪያ ቆመው ነበር፤ በዙፋኑ ፊት በግንባራቸው ተደፍተው ለእግዚአብሔር ሰገዱ፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ራእይ 7