1. ከዚህ በኋላ ታላቅ ሥልጣን ያለው ሌላ መልአክ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ፤ ከክብሩም ነጸብራቅ የተነሣ ምድር በራች፤
2. እርሱም በብርቱ ድምፅ እንዲህ ብሎ ጮኸ፤“ታላቂቱ ባቢሎን ወደቀች! ወደቀች!የአጋንንት መኖሪያ፣የርኩሳን መናፍስት ሁሉ መጠጊያ፣የርኩስና የአስጸያፊ ወፎች ሁሉ መጠለያ ሆነች።
3. ሕዝቦች ሁሉ የዝሙቷን ቍጣ ወይን ጠጅ ጠጥተዋልና፤የምድር ነገሥታት ከእርሷ ጋር አመንዝረዋል፤የምድርም ነጋዴዎች ከብዙ ምቾቷ ኀይልየተነሣ በልጽገዋል።”