ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ማቴዎስ 5:1-9 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ብዙ ሕዝብ እንደ ተሰበሰበ ባየ ጊዜ፣ ወደ ተራራ ወጣና ተቀመጠ፤ ደቀ መዛሙርቱም ወደ እርሱ መጡ።

2. እንዲህም እያለ ያስተምራቸው ጀመር፤

3. “በመንፈስ ድኾች የሆኑ ብፁዓን ናቸው፤ መንግሥተ ሰማይ የእነርሱ ናትና።

4. የሚያዝኑ ብፁዓን ናቸው፤ መጽናናትን ያገኛሉና።

5. የዋሆች ብፁዓን ናቸው፤ ምድርን ይወርሳሉና።

6. ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ ብፁዓን ናቸው፤ ይጠግባሉና።

7. ምሕረት የሚያደርጉ ብፁዓን ናቸው፤ ምሕረትን ያገኛሉና።

8. ልባቸው ንጹሕ የሆነ ብፁዓን ናቸው፤ እግዚአብሔርን ያዩታልና።

9. ሰላምን የሚያወርዱ ብፁዓን ናቸው፤ የእግዚአብሔር ልጆች ተብለው ይጠራሉና።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ማቴዎስ 5