ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሐዋርያት ሥራ 13:33-39 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

33. ኢየሱስንም ከሙታን በማስነሣቱ ለእነርሱ የገባውን ቃል ለእኛ ለልጆቻቸው ፈጽሞአል፤ ይኸውም በሁለተኛው መዝሙር እንዲህ ተብሎ ተጽፎአል፤“ ‘አንተ ልጄ ነህ፤እኔ ዛሬ ወለድሁህ።’

34. ደግሞም፣ እርሱ እንዳልበሰበሰና እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው ለማረጋገጥ እንዲህ ብሎአል፤“ ‘የተቀደሰውንና የታመነውን፣ የዳዊትን በረከት እሰጣችኋለሁ።’

35. ስለዚህ በሌላም ስፍራ፣“ ‘ቅዱስህ መበስበስን እንዲያይ አትፈቅድም’ ይላል።

36. “ዳዊት በራሱ ዘመን የእግዚአብሔርን ፈቃድ ካገለገለ በኋላ አንቀላፍቶአል፤ ከአባቶቹም ጋር ተቀብሮ ሥጋው በስብሶአል።

37. እግዚአብሔር ከሙታን ያስነሣው እርሱ ግን መበስበስን አላየም።

38. እንግዲህ ወንድሞች ሆይ፤ የኀጢአት ይቅርታ የሚገኘው በኢየሱስ በኩል መሆኑ እንደ ተሰበከላችሁ ዕወቁ፤

39. በእርሱ የሚያምን ሁሉ በሙሴ ሕግ በኩል ማግኘት ያልተቻለውን ጽድቅ ያገኛል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሐዋርያት ሥራ 13