ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሉቃስ 22:64-71 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

64. ዐይኑንም ሸፍነው፣ “እስቲ ትንቢት ተናገር፤ የመታህ ማነው? እያሉ ይጠይቁት ነበር።

65. ሌላም ብዙ የስድብ ቃል እየተናገሩ ያቃልሉት ነበር።

66. በነጋም ጊዜ፣ የሕዝብ ሽማግሌዎች፣ የካህናት አለቆችና ጸሐፍት ተሰበሰቡ፤ ኢየሱስንም በሸንጎአቸው ፊት አቀረቡት።

67. እነርሱም፣ “አንተ ክርስቶስ ነህን? እስቲ ንገረን” አሉት።ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፤ “ብነግራችሁ አታምኑኝም፤

68. ብጠይቃችሁም አትመልሱም።

69. ነገር ግን ከአሁን ጀምሮ የሰው ልጅ በእግዚአብሔር ኀይል ቀኝ ይቀመጣል።”

70. በዚህ ጊዜ ሁሉም፣ “ታዲያ፣ አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህን?” አሉት።እርሱም፣ “መሆኔን እኮ እናንተው ተናገራችሁት” አላቸው።

71. እነርሱም፣ “ከእንግዲህ ሌላ ምስክር ምን ያስፈልገናል? ራሳችን ከገዛ አንደበቱ ሰምተናልና” አሉ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሉቃስ 22