ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሉቃስ 22:14-19 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

14. ሰዓቱም በደረሰ ጊዜ ኢየሱስ ከሐዋርያቱ ጋር በማእድ ተቀመጠ፤

15. እንዲህም አላቸው፤ “መከራ ከመቀበሌ በፊት ይህን ፋሲካ አብሬያችሁ ለመብላት በጣም ስመኝ ነበር፤

16. እላችኋለሁ፤ በእግዚአብሔር መንግሥት የዚህ ትርጒም እስኪፈጸም ድረስ ይህን ፋሲካ ዳግመኛ አልበላም።”

17. ጽዋውን ተቀብሎ ካመሰገነ በኋላ እንዲህ አላቸው፤ “እንካችሁ፤ ሁላችሁ ከዚህ ተካፈሉ፤

18. እላችኋለሁና፤ ከአሁን ጀምሮ የእግዚአብሔር መንግሥት እስከምትመጣ ድረስ፣ ከዚህ ወይን ፍሬ አልጠጣም።”

19. እንጀራንም አንሥቶ አመሰገነ፤ ቈርሶም ሰጣቸውና፣ “ይህ ስለ እናንተ የሚሰጥ ሥጋዬ ነው፤ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት” አለ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሉቃስ 22