ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሉቃስ 20:1-7 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. አንድ ቀን ኢየሱስ ሕዝቡን በቤተ መቅደስ ሲያስተምርና ወንጌልን ሲሰብክ የካህናት አለቆች፣ ጸሐፍትና ሽማግሌዎች ተሰብስበው ወደ እርሱ መጡ፤

2. እነርሱም፣ “እነዚህን ነገሮች የምታደርገው በምን ሥልጣን እንደሆነ ንገረን፤ ሥልጣንስ የሰጠህ ለመሆኑ እርሱ ማን ነው?” ብለው ጠየቁት።

3. እርሱም እንዲህ ሲል መለሰላቸው፤ “እኔም አንድ ጥያቄ ልጠይቃችሁ፤ እስቲ መልሱልኝ፤

4. የዮሐንስ ጥምቀት ከሰማይ ነበር ወይስ ከሰው?”

5. እነርሱም እንዲህ ብለው እርስ በርስ ተመካከሩ፤ “ ‘ከሰማይ’ ብንል፣ ‘ታዲያ፣ ለምን አላመናችሁበትም?’ ይለናል፤

6. ‘ከሰው’ ብንል ሕዝቡ ሁሉ ዮሐንስ ነቢይ መሆኑን ስለ ሚያምኑ በድንጋይ ይወግሩናል።”

7. ስለዚህ፣ “ከየት እንደሆነ አናውቅም” ብለው መለሱለት።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሉቃስ 20