ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሉቃስ 1:64-73 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

64. ወዲያውም አፉ ተከፈተ፤ አንደበቱ ተፈታ፤ እግዚአብሔርንም እያመሰገነ መናገር ጀመረ።

65. ጎረቤቶቹም ሁሉ በፍርሀት ተሞሉ፤ ይህም ሁሉ ነገር በደጋማው የይሁዳ ምድር ሁሉ ተወራ።

66. ይህንም የሰሙ ሁሉ፣ “ይህ ሕፃን ምን ሊሆን ይሆን?” እያሉ ነገሩን በልባቸው ያዙ፤ የጌታ እጅ በርግጥ ከእርሱ ጋር ነበርና።

67. የሕፃኑም አባት ዘካርያስ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ እንዲህ ሲል ትንቢት ተናገረ፤

68. “የእስራኤል አምላክ፣ ጌታ ይመስገን፤መጥቶ ሕዝቡን ተቤዥቶአልና።

69. በባሪያው በዳዊት ቤት፣የድነት ቀንድ አስነሥቶልናል፤

70. ይህም ጥንት በቅዱሳን ነቢያቱ አፍ እንደ ተናገረው፣

71. ማዳኑም ከጠላቶቻችንና፣ከተፃራሪዎቻችን ሁሉ እጅ ነው፤

72. ይህንም ያደረገው ለአባቶቻችን ምሕረቱን ለማሳየት፣ቅዱስ ኪዳኑን ለማስታወስ፣

73. ለአባታችን ለአብርሃም የማለውን መሐላ ለማሰብ፣

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሉቃስ 1