ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

2 ዮሐንስ 1:9-13 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

9. በክርስቶስ ትምህርት የማይኖርና ከትምህርቱ የሚወጣ ሁሉ አምላክ የለውም፤ በክርስቶስ ትምህርት የሚኖር ግን አብም ወልድም አለው።

10. ማንም ወደ እናንተ ቢመጣ፣ ይህንንም ትምህርት ባያመጣ በቤታችሁ አትቀበሉት፤ ሰላምም አትበሉት፤

11. የሚቀበለው ሰው፣ የክፉ ሥራው ተባባሪ ይሆናልና።

12. የምጽፍላችሁ ብዙ ነገር ነበረኝ፤ ይሁን እንጂ በወረቀትና በቀለም እንዲሆን አልፈልግም፤ ዳሩ ግን ደስታችን ፍጹም ይሆን ዘንድ ወደ እናንተ መጥቼ ፊት ለፊት ላነጋግራችሁ ተስፋ አደርጋለሁ።

13. የተመረጠችው የእኅትሽ ልጆች ሰላምታ ያቀርቡልሻል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ 2 ዮሐንስ 1