ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

1 ጴጥሮስ 2:1-7 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. እንግዲህ ክፋትን ሁሉ፣ ማታለልን ሁሉ፣ ግብዝነትን፣ ቅናትንና ሐሜትን ሁሉ አስወግዱ፤

2. በድነታችሁ እንድታድጉ፣ አዲስ እንደ ተወለዱ ሕፃናት ንጹሑን መንፈሳዊ ወተት ተመኙ፤

3. ጌታ መልካም መሆኑን ቀምሳችኋልና።

4. በሰው ዘንድ ወደ ተናቀው፣ በእግዚአብሔር ዘንድ ግን ወደ ተመረጠውና ክቡር ወደ ሆነው ወደዚህ ሕያው ድንጋይ እየቀረባችሁ፣

5. እናንተ ደግሞ፣ በኢየሱስ ክርስቶስ አማካይነት እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ መንፈሳዊ መሥዋዕት ታቀርቡ ዘንድ፣ ቅዱሳን ካህናት ለመሆን እንደ ሕያዋን ድንጋዮች መንፈሳዊ ቤት ለመሆን ትሠራላችሁ።

6. ምክንያቱም በመጽሐፍ እንዲህ ተብሎ ተጽፎአልና፤“እነሆ፤ የተመረጠና ክቡር የማእዘን ድንጋይ፣በጽዮን አኖራለሁ፤በእርሱም የሚያምን፣ ከቶ አያፍርም።”

7. እንግዲህ ለእናንተ ለምታምኑት ይህ ድንጋይ ክቡር ነው፤ ለማያምኑት ግን፣“ግንበኞች የናቁት ድንጋይ፣እርሱ የማእዘን ራስ ሆነ።”

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ 1 ጴጥሮስ 2