ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

1 ቆሮንቶስ 15:32-37 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

32. በኤፌሶን ከአራዊት ጋር የታገልሁት ለሰው አስተያየት ብቻ ከሆነ ትርፌ ምንድን ነው? ሙታን የማይነሡ ከሆነ፤“ነገ ስለምንሞት፣እንብላ፣ እንጠጣ፤” እንደሚሉት መሆናችን ነው።

33. አትሳቱ፤ “መጥፎ ጓደኝነት መልካሙን ጠባይ ያበላሻል።”

34. ወደ ሰከነ ልቦናችሁ ተመለሱ፤ ኀጢአትንም አትሥሩ፤ እግዚአብሔርን የማያውቁ አሉና ይህንንም የምለው ላሳፍራችሁ ነው።

35. ነገር ግን፣ “ሙታን እንዴት ይነሣሉ? የሚመጡትስ በምን ዐይነት አካል ነው?” የሚል ሰው ሊኖር ይችላል።

36. አንተ ሞኝ! የምትዘራው ካልሞተ ሕይወት አያገኝም።

37. የምትዘራውም የስንዴ ወይም የሌላ ዐይነት ዘር ቅንጣት ብቻ እንጂ ወደ ፊት የምታገኘውን አካል አይደለም።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ 1 ቆሮንቶስ 15