ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘፍጥረት 46:7-19 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

7. ወደ ግብፅም የወረደው፣ ወንዶች ልጆቹንና ወንዶች የልጅ ልጆቹን፣ ሴቶች ልጆቹንና ሴቶች የልጅ ልጆቹን ማለት ዘሮቹን ሁሉ ይዞ ነው።

8. ወደ ግብፅ የወረዱት የእስራኤል ልጆች፣ ያዕቆብ ዘሮቹ እነዚህ ናቸው፦የያዕቆብ የበኵር ልጅ ሮቤል።

9. የሮቤል ልጆች፦ሄኖኅ፣ ፈሉሶ፣ አስሮን እና ከርሚ ናቸው።

10. የስምዖን ልጆች፦ይሙኤል፣ ያሚን፣ ኦሃድ፣ ያኪን፣ጾሐርና ከከነዓናዊቷ ሴት የተወለደውሳኡል ናቸው።

11. የሌዊ ልጆች፦ጌድሶን፣ ቀዓትና ሜራሪ ናቸው።

12. የይሁዳ ልጆች፦ዔር፣ አውናን፣ ሴሎም፣ ፋሬስ እናዛራ ናቸው። ነገር ግን ዔርና አውናንበከነዓን ምድር ሞቱ።

13. የይሳኮር ልጆች፦ቶላ፣ ፉዋ፣ ዮብና ሺምሮን ናቸው፤

14. የዛብሎን ልጆች፦ሴሬድ፣ ኤሎንና ያሕልኤል ናቸው፤

15. እነዚህ ወንዶች ልጆች ያዕቆብ በሰሜን ምዕራብ መስጴጦምያ ሳለ፣ ልያ የወለደችለት ናቸው። ሴቷን ዲናን ጨምሮ፣ የወንዶችና የሴቶች ልጆቹ ቍጥር ሠላሳ ሦስት ነው።

16. የጋድ ልጆች፦ጽፎን፣ ሐጊ፣ ሹኒ፣ ኤስቦን፣ዔሪ፣ አሮዲና አርኤሊ ናቸው፤

17. የአሴር ልጆች፦ዪምና፣ የሱዋ፣ የሱዊና በሪዓ ናቸው፤እኅታቸውም ሤራሕ ናት፤የበሪዓ ልጆች፦ሐቤርና መልኪኤል ናቸው፤

18. እነዚህ ዐሥራ ስድስት ልጆች ሁሉ፣ ላባ ለልጁ ለልያ ከሰጣት ከዘለፋ ላይ ያዕቆብ የወለዳቸው ናቸው።

19. የያዕቆብ ሚስት የራሔል ልጆች፦ዮሴፍና ብንያም ናቸው፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘፍጥረት 46