ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘፍጥረት 36:21-39 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

21. ዲሶን፣ ኤጽርና ዲሳን፤ እነዚህ በኤዶም የነበረው የሴይር ልጆች፣ የሖሪውያን የነገድ አለቆች ነበሩ።

22. የሎጣን ልጆች፦ሖሪና ሔማም፤ የሎጣንም እኅት ቲምናዕ ትባል ነበር።

23. የሦባል ልጆች፦ዓልዋን፣ ማኔሐት፣ ዔባል፣ ስፎና አውናም፤

24. የፅብዖን ልጆች፦አያና ዓና፤ ይህ ዓና የአባቱን የፅብዖንን አህዮች ሲጠብቅ፣ የፍል ውሃ ምንጮችን በምድረ በዳ ያገኘ ሰው ነው።

25. የዓና ልጆች፦ዲሶንና የዓና ሴት ልጅ አህሊባማ፤

26. የዲሶን ልጆች፦ሔምዳን፣ ኤስባን፣ ይትራንና ክራን፤

27. የኤጽር ልጆች፦ቢልሐን፣ ዛዕዋንና ዓቃን፤

28. የዲሳን ልጆች፦ዑፅና አራን።

29. የሖሪውያን የነገድ አለቆች እነዚህ ነበሩ፦ሎጣን፣ ሦባል፣ ፅብዖን፣ ዓና፣

30. ዲሶን፣ ኤጽርና ዲሳን፤ እነዚህ በሴይር ምድር እንደየነገዳቸው የሖሪውያን የነገድ አለቆች ነበሩ።

31. ንጉሥ በእስራኤል ከመንገሡ በፊት፣ በኤዶም የነገሡ ነገሥታት እነዚህ ነበሩ፦

32. የቢዖር ልጅ ባላቅ በኤዶም ነበር፤ የከተማውም ስም ዲንሃባ ይባል ነበር።

33. ባላቅ ሲሞት፣ የባሶራው የዛራ ልጅ ኢዮባብ በምትኩ ነገሠ።

34. ኢዮባብ ሲሞት፣ የቴማኒው ሑሳም በምትኩ ነገሠ።

35. ሑሳም ሲሞት፣ የምድያምን ሰዎች በሞዓብ ምድር ድል ያደረጋቸው የባዳድ ልጅ ሃዳድ በምትኩ ነገሠ፤ የከተማውም ስም ዓዊት ይባል ነበር።

36. ሃዳድ ሲሞት፣ የመሥሬቃው ሠምላ በምትኩ ነገሠ።

37. ሠምላ ሲሞት፣ በወንዙ አጠገብ ያለው የርሆቦቱ ሳኦል በምትኩ ነገሠ።

38. ሳኦል ሲሞት፣ የዓክቦር ልጅ በኣልሐናን በምትኩ ነገሠ።

39. የዓክቦር ልጅ በኣልሐናን ሲሞት፣ ሃዳር በምትኩ ነገሠ፤ የከተማውም ስም ፋዑ ይባል ነበር፤ የሚስቱም ስም መሄጣብኤል ሲሆን፣ እርሷም የሜዛሃብ ልጅ መጥሬድ የወለደቻት ነበረች።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘፍጥረት 36