ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘፍጥረት 32:26-30 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

26. በዚያን ጊዜ ሰውየው፣ “እንግዲህ መንጋቱ ስለ ሆነ ልቀቀኝና ልሂድ” አለው።ያዕቆብም፣ “ካልባረክኸኝ አልለቅህም” አለው።

27. ሰውየውም፣ “ስምህ ማን ነው?” አለው።እርሱም፣ “ያዕቆብ ነው” አለ።

28. ሰውየውም፣ “ከእግዚአብሔርም (ኤሎሂም)፣ ከሰዎችም ጋር ታግለህ አሸንፈሃልና ከእንግዲህ ስምህ እስራኤል እንጂ፣ ያዕቆብ አይባልም” አለው።

29. ያዕቆብም፣ “እባክህ ስምህን ንገረኝ” ብሎ ጠየቀው።ሰውዬውም፣ “ስሜን ለማወቅ ለምን ፈለግህ?” አለው፤ በዚያም ስፍራ ባረከው።

30. ስለዚህ ያዕቆብ፣ “እግዚአብሔርን (ኤሎሂም) ፊት ለፊት አይቼ እንኳ ሕይወቴ ተርፋለች” ሲል፣ የዚያን ቦታ ስም ጵኒኤል አለው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘፍጥረት 32