ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘፍጥረት 3:17-23 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

17. አዳምንም እንዲህ አለው፤ “የሚስትህን ቃል ሰምተህ፣ ‘ከእርሱ አትብላ’ ብዬ ያዘዝሁህን ዛፍ በልተሃልና፣“ከአንተ የተነሣ ምድር የተረገመች ትሁን፤በሕይወትህ ዘመን ሁሉምግብህን ጥረህ ግረህ ከእርሷ ታገኛለህ።

18. ምድርም እሾኽና አሜከላታበቅልብሃለች፤ከቡቃያዋም ትበላለህ።

19. ከምድር ስለ ተገኘህ፣ወደ መጣህበት መሬት እስክትመለስድረስእንጀራህን በፊትህ ላብ ትበላለህ፤ዐፈር ነህናወደ ዐፈር ትመለሳለህ።”

20. አዳምም የሕያዋን ሁሉ እናት ናትና ሚስቱን ሔዋን ብሎ ጠራት።

21. እግዚአብሔር አምላክ (ያህዌ ኤሎሂም) ከቈዳ ልብስ አዘጋጅቶ አዳምንና ሚስቱን አለበሳቸው።

22. ከዚያም እግዚአብሔር አምላክ (ያህዌ ኤሎሂም)፣ “ሰው መልካምንና ክፉውን ለይቶ በማወቅ ረገድ አሁን ከእኛ እንደ አንዱ ሆኗል፤ አሁን ደግሞ እጁን ዘርግቶ ከሕይወት ዛፍ ቀጥፎ እንዳይበላ፣ ለዘላለምም እንዳይኖር ይከልከል” አለ።

23. ስለዚህ የተገኘበትን ምድር እንዲያርስ፣ እግዚአብሔር አምላክ (ያህዌ ኤሎሂም) ሰውን ከዔድን የአትክልት ስፍራ አስወጣው፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘፍጥረት 3