ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘፍጥረት 24:55-60 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

55. ወንድሟና እናቷም፣ “ልጂቷ ከእኛ ጋር ቢያንስ ዐሥር ቀን ያህል ትቈይና ከዚያ በኋላ ልትሄድ ትችላለች።” ብለው መለሱ።

56. እርሱ ግን፣ “እግዚአብሔር (ያህዌ) መንገዴን አቅንቶልኛልና አታዘግዩኝ፤ ወደ ጌታዬ እንድመለስ አሰናብቱኝ” አላቸው።

57. እነርሱም፣ “ለማናቸውም ልጂቱን እንጥራትና ትጠየቅ” አሉ።

58. ስለዚህ ርብቃን ጠርተው፣ “ከዚህ ሰው ጋር መሄድ ትፈቅጃለሽ?” ሲሉ ጠየቋት።እርሷም፣ “አዎን፤ እሄዳለሁ” አለች።

59. ከዚያም እኅታቸውን ርብቃን ከሞግዚቷ ጋር፣ እንዲሁም የአብርሃምን አገልጋይና አብረውት የነበሩትን ሰዎች አሰናበቷቸው።

60. ርብቃንም እንዲህ ብለው መረቋት፤“እኅታችን ሆይ፤ እልፍ አእላፋት ሁኚ፤ዘርሽ የጠላቶቹን ደጆች ይውረስ”።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘፍጥረት 24