ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘፍጥረት 11:12-27 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

12. አርፋክስድ በ35 ዓመቱ ሳላን ወለደ፤

13. ሳላንን ከወለደ በኋላ አርፋክስድ 403 ዓመት ኖረ፤ ሌሎች ወንዶችና ሴቶችን ወለደ።

14. ሳላ በ30 ዓመቱ ዔቦርን ወለደ፤

15. ዔቦርን ከወለደ በኋላ ሳላ 403 ዓመት ኖረ፤ ሌሎች ወንዶችና ሴቶች ልጆችን ወለደ።

16. ዔቦር በ34 ዓመቱ ፋሌቅን ወለደ፤

17. ፋሌቅን ከወለደ በኋላ ዔቦር 430 ዓመት ኖረ፤ ሌሎች ወንዶችና ሴቶች ልጆችን ወለደ።

18. ፋሌቅ በ30 ዓመቱ ራግውን ወለደ፤

19. ራግውንን ከወለደ በኋላ ፋሌቅ 209 ዓመት ኖረ፤ ሌሎች ወንዶችና ሴቶች ልጆችን ወለደ።

20. ራግው በ32 ዓመቱ ሴሮሕን ወለደ፤

21. ሴሮሕን ከወለደ በኋላ ራግው 207 ዓመት ኖረ፤ ሌሎች ወንዶችና ሴቶች ልጆችን ወለደ።

22. ሴሮሕ በ30 ዓመቱ ናኮርን ወለደ፤

23. ናኮርን ከወለደ በኋላ ሴሮሕ 200 ዓመት ኖረ፤ ሌሎች ወንዶችና ሴቶች ልጆችን ወለደ።

24. ናኮር በ29 ዓመቱታራን ወለደ፤

25. ታራን ከወለደ በኋላ ናኮር 119 ዓመት ኖረ፤ ሌሎች ወንዶችና ሴቶች ልጆችን ወለደ።

26. ታራ 70 ዓመት ከሆነው በኋላ አብራምን፣ ናኮርንና ሐራንን ወለደ።

27. የታራ ትውልድ ይህ ነው፦ታራ፣ አብራምን ናኮርንና ሐራንን ወለደ፤ሐራንም ሎጥን ወለደ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘፍጥረት 11