ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘፍጥረት 11:11-19 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

11. ሴም፣ አርፋክስድን ከወለደ በኋላ 500 ዓመት ኖረ፤ ሌሎች ወንዶችና ሴቶች ልጆችን ወለደ።

12. አርፋክስድ በ35 ዓመቱ ሳላን ወለደ፤

13. ሳላንን ከወለደ በኋላ አርፋክስድ 403 ዓመት ኖረ፤ ሌሎች ወንዶችና ሴቶችን ወለደ።

14. ሳላ በ30 ዓመቱ ዔቦርን ወለደ፤

15. ዔቦርን ከወለደ በኋላ ሳላ 403 ዓመት ኖረ፤ ሌሎች ወንዶችና ሴቶች ልጆችን ወለደ።

16. ዔቦር በ34 ዓመቱ ፋሌቅን ወለደ፤

17. ፋሌቅን ከወለደ በኋላ ዔቦር 430 ዓመት ኖረ፤ ሌሎች ወንዶችና ሴቶች ልጆችን ወለደ።

18. ፋሌቅ በ30 ዓመቱ ራግውን ወለደ፤

19. ራግውንን ከወለደ በኋላ ፋሌቅ 209 ዓመት ኖረ፤ ሌሎች ወንዶችና ሴቶች ልጆችን ወለደ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘፍጥረት 11