ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘፍጥረት 10:18-28 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

18. የአራዴዎ ናውያን፣ የሰማሪናውያን፣ የአማቲያውያን አባት ነበረ።ከጊዜ በኋላ የከነዓን ጐሣዎች በየስፍራው ተሠራጩ፤

19. የከነዓን ወሰን ከሲዶና አንሥቶ በጌራራ በኩል እስከ ጋዛ ይደርሳል፤ ከዚያም በሰዶም በኩል ገሞራን፣ አዳማንና ሰቦይን ይዞ እስከ ላሣ ይዘልቃል።

20. እነዚህም በየጐሣቸውና በየቋንቋቸው፣ በየምድራቸውና በየነገዳቸው ይኖሩ የነበሩ የካም ዝርያዎች ናቸው።

21. ለያፌት ታላቅ ወንድም ለሴም ደግሞ ወንዶች ልጆች ተወለዱለት፤ እርሱም የዔ ቦር ልጆች ሁሉ ቅደመ አያት ነው።

22. የሴም ልጆች፦ኤላም፣ አሦር፣ አርፋክስድ፣ ሉድ፣ አራም ናቸው።

23. የአራም ልጆች፦ዑፅ፣ ሁል፣ ጌቴር፣ ሞሶሕ ናቸው።

24. አርፋክስድ ሳላን ወለደ፤ሳላም ዔቦርን ወለደ።

25. ለዔቦርም ሁለት ወንዶች ልጆች ተወለዱለት፤አንደኛው ልጅ በዘመኑ ምድር ተከፍላ ስለ ነበር ፍሌቅ ተባለ፤ ወንድሙም ዮቅጣን ተባለ።

26. ዮቅጣንም፦ የኤልሞሳድ፣ የሣሌፍ፣ የሐስረ ሞት፣ የያራሕ፣

27. የሀደራም፣ የአውዛል፣ የደቅላ አባት ነበረ፤

28. እንዲሁም የዖባል፣ የአቢማኤል፣ የሳባ፣

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘፍጥረት 10