ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘፀአት 21:11-18 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

11. እነዚህን ሦስት ነገሮች የማያሟላላት ቢሆን፣ ያላንዳች የገንዘብ ክፍያ በነጻ መሄድ ይኖርባታል።

12. “ሰውን ደብድቦ የገደለ ሞት ይገባዋል።

13. ሆኖም እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ፈቅዶ ሰውየው ሳያውቅ በድንገት አድርጎት ከሆነ፣ እኔ ወደምወስነው ስፍራ ይሽሽ።

14. አንድ ሰው በተንኰል ሆን ብሎ ሌላውን ቢገድል፣ ከመሠዊያዬ ተወስዶ ይገደል።

15. “አባቱን ወይንም እናቱን የሚመታ ይገደል።

16. “አንዱ ሌላውን ጠልፎ የሸጠ ወይም በተያዘ ጊዜ ከእጁ ላይ የተገኘበት ይገደል።

17. “አባቱን ወይንም እናቱን የሚሰድብ ይገደል።

18. ሰዎች ተጣልተው አንዱ ሌላውን በድንጋይ ወይም በቡጢ ቢመታውና ተመቺው ሳይሞት በአልጋ ላይ ቢውል፣

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘፀአት 21