ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘዳግም 33:8-20 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

8. ስለ ሌዊም እንዲህ አለ፦“ቱሚምህና ኡሪምህ፣ለምትወደው ሰው ይሁን፤ማሳህ በተባለው ቦታ ፈተንኸው፤በመሪባም ውሃ ከእርሱ ጋር ተከራከርህ።

9. ስለ አባቱና ስለ እናቱ ሲናገርም፣‘ስለ እነርሱ ግድ የለኝም’ አለ።ወንድሞቹን አልለያቸውም፤ልጆቹንም አላወቃቸውም።ለቃልህ ማን ጥንቃቄ አደረገ፤ኪዳንህንም ጠበቀ።

10. ሥርዐትህን ለያዕቆብ፣ሕግህንም ለእስራኤል ያስተምራል።ዕጣን በፊትህ፣የሚቃጠለውን መሥዋዕት ሁሉ በመሠዊያህ ላይ ያቀርባል።

11. እግዚአብሔር (ያህዌ) ሆይ፤ ኀይሉን ሁሉ ባርክለት፤በእጁ ሥራ ደስ ይበልህ፤በእርሱ ላይ የሚነሡበትን ሽንጣቸውን ቊረጠው፤ጠላቶቹንም እንዳያንሠራሩ አድርገህ ምታቸው።”

12. ስለ ብንያም እንዲህ አለ፦“የእግዚአብሔር (ያህዌ) ወዳጅ የሆነ በእርሱ ተጠብቆ በሰላም ይረፍ፤ቀኑን ሙሉ ይጋርደዋልና፤ እግዚአብሔር (ያህዌ) የሚወደውም ሰው በትከሻዎቹ መካከል ያርፋል።”

13. ስለ ዮሴፍ ደግሞ እንዲህ አለው፦“እግዚአብሔር (ያህዌ) ምድሩን ይባርክ፤ድንቅ የሆነውን ጠል ከላይ ከሰማይ በማውረድ፣ከታች የተንጣለለውን ጥልቅ ውሃ በመስጠት፤

14. ፀሓይ በምታስገኘው ምርጥ ፍሬ፣ጨረቃም በምትሰጠው እጅግ መልካም ነገር፤

15. ከጥንት ተራሮች በተገኘ ምርጥ ስጦታ፣በዘላለማዊ ኰረብቶች ፍሬያማነት፤

16. ምድር በምታስገኘው ምርጥ ስጦታና በሙላቷ፣በሚቃጠለው ቊጥቋጦም ውስጥ በነበረው በእርሱ ሞገስ።እነዚህ ሁሉ በወንድሞቹ መካከል ገዥ በሆነው፣በዮሴፍ ዐናት ላይ ይውረዱ።

17. በግርማው እንደ በኵር ኰርማ ነው፤ቀንዶቹም የጐሽ ቀንዶች ናቸው።በእነርሱም ሕዝቦችን፣በምድር ዳርቻ ላይ ያሉትን እንኳ ሳይቀር ይወጋል፤እነርሱም የኤፍሬም ዐሥር ሺዎቹ ናቸው፤የምናሴም ሺዎቹ እንደዚሁ ናቸው።”

18. ስለ ዛብሎንም እንዲህ አለ፦“ዛብሎን ሆይ፤ ወደ ውጭ በመውጣትህ፣አንተም ይሳኮር በድንኳኖችህ ውስጥ ደስ ይበልህ፤

19. አሕዛብን ወደ ተራራው ይጠራሉ፤በዚያም የጽድቅን መሥዋዕት ያቀርባሉ።በባሕሮች ውስጥ ያለውን በተትረፈረፈ ብልጽግና፣በአሸዋውም ውስጥ የተደበቀውን ሀብት ይደሰቱበታል።”

20. ስለ ጋድም እንዲህ አለ፦“የጋድን ግዛት የሚያሰፋ የተመሰገነ ነው!ክንድንና ራስን በመገነጣጠል፣ጋድ እንደ አንበሳ በዚያ ይኖራል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘዳግም 33