ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘዳግም 32:17-29 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

17. አምላክ ላልሆኑ አጋንንት፦ላላወቋቸው አማልክት፣ከጊዜ በኋላ ለተነሡ አማልክት፣አባቶቻችሁ ላልፈሯቸው አማልክት ሠዉ።

18. አባት የሆነህን ዐለት ከዳኸው፤የወለደህን አምላክ (ኤሎሂም) ረሳኸው።

19. እግዚአብሔር (ያህዌ) ይህን አይቶ ናቃቸው፤በወንድና በሴት ልጆቹ ተቈጥቶአልና።

20. እርሱም፣ “ፊቴን ከእነርሱ እሰውራለሁ፤”“መጨረሻቸው ምን እንደሚሆንም አያለሁ አለ፤ጠማማ ትውልድ፣የማይታመኑም ልጆች ናቸውና።

21. አምላክ ባልሆነው አስቀኑኝ፤በከንቱ ጣዖቶቻቸው አስቈጡኝ።እኔም ሕዝብ ባልሆነው አስቀናቸዋለሁ።በማያስተውልም ሕዝብ አስቈጣቸዋለሁ።

22. በቊጣዬ እሳት ተቀጣጥሎአልና፤እርሱ እስከ ሲኦል ዘልቆ ይነዳል።ምድርን እስከ ሰብሏ ይበላል፤የተራሮችንም መሠረት ያቀጣጥላል።

23. “በመዓት ላይ መዓት አመጣባቸዋለሁ።ፍላጻዬንም በእነርሱ ላይ እጨርሳለሁ።

24. የሚያጠፋ ራብ፣ በልቶ የሚጨርስ ቸነፈርና ከባድመቅሠፍት እሰድባቸዋለሁ፤የአራዊትን ሹል ጥርስ፣ በምድር የሚሳብ የእባብ መርዝምእሰድባቸዋለሁ።

25. ሰይፍ መንገድ ላይ ያስቀራቸዋል፤ቤታቸውም ውስጥ ድንጋጤ ይነግሣል፤ጐልማሳውና ልጃገረዷ፣ሕፃኑና ሽማግሌው ይጠፋሉ።

26. እበትናቸዋለሁ፤ ከሰዎችም መካከል መታሰቢያቸውንአጠፋለሁ አልሁ፤

27. ነገር ግን ጠላቶቻቸው እንዳይታበዩ፣‘ድል ያደረገችው እጃችን እንጂ፣ እግዚአብሔር (ያህዌ) ይህን ሁሉ አላደረገም እንዳይሉ፣’ ”የጠላትን መነሣሣት ሠጋሁ።

28. አእምሮ የጐደላቸው፣ማስተዋልም የሌላቸው ናቸው።

29. አስተዋዮች ቢሆኑ ኖሮ ይህን በተገነዘቡ፣መጨረሻቸውም ምን እንደሚሆን ባስተዋሉ ነበር።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘዳግም 32