ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘኁልቍ 33:7-13 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

7. ከኤታም ተነሥተው ከበኣልዛፎን በስተ ምሥራቅ ወዳለችው ወደ ፊሀሒሮት በመመለስ በሚግዶል አጠገብ ሰፈሩ።

8. ከፊሀሒሮት ተነሥተው በባሕሩ ውስጥ በማለፍ ወደ ምድረ በዳው ሄዱ፤ ከዚያም በኤታም ምድረ በዳ ሦስት ቀን ተጒዘው በማራ ሰፈሩ።

9. ከማራ ተነሥተው ዐሥራ ሁለት የውሃ ምንጮችና ሰባ የተምር ዛፎች ወደነበሩበት ወደ ኤሊም መጥተው በዚያ ሰፈሩ።

10. ከኤሊም ተነሥተው በቀይ ባሕር አጠገብ ሰፈሩ።

11. ከቀይ ባሕር ተነሥተው በሲን ምድረ በዳ ሰፈሩ።

12. ከሲን ምድረ በዳ ተነሥተው በራፍቃ ሰፈሩ።

13. ከራፍቃ ተነሥተው በኤሉስ ሰፈሩ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘኁልቍ 33