ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘኁልቍ 33:41-49 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

41. እነርሱም ከሖር ተራራ ተነሥተው በሴልሞና ሰፈሩ።

42. ከሴልሞና ተነሥተው በፋኖን ሰፈሩ።

43. ከፋኖን ተነሥተው በአቦት ሰፈሩ።

44. ከአቦት ተነሥተው በሞዓብ ዳርቻ በምትገኘው በኢየአባሪም ሰፈሩ።

45. ከኢይም ተነሥተው በዲቦንጋድ ሰፈሩ።

46. ከዲቦንጋድ ተነሥተው በዓልሞን ዲብላታይም ሰፈሩ።

47. ከዓልሞንዲብላታይም ተነሥተው በናባው አጠገብ በሚገኙት በዓብሪም ተራራዎች ላይ ሰፈሩ።

48. ከዓብሪም ተራራዎች ተነሥተው ከኢያሪኮ ማዶ በዮርዳኖስ ወንዝ አጠገብ ባለው በሞዓብ ሜዳ ላይ ሰፈሩ።

49. እዚያም በዮርዳኖስ ወንዝ አጠገብ በሞዓብ ሜዳ ከቤት የሺሞት እስከ አቤልስጢም ባለው ስፍራ ሰፈሩ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘኁልቍ 33