ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘኁልቍ 21:20-31 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

20. ከባሞትም ፈስጋ ላይ ሆኖ ምድረ በዳው ቊልቊል ወደሚታይበት በሞዓብ ወደሚገኘው ሸለቆ ተጓዙ።

21. እስራኤል ወደ አሞራውያን ንጉሥ ወደ ሴዎን እንዲህ የሚሉ መልእክተኞች ላከ፤

22. “በአገርህ አልፈን እንድንሄድ ፍቀድልን፤ ወደ የትኛውም ዕርሻ ሆነ የወይን አትክልት አንገባም፤ ወይም ከየትኛውም ጒድጓድ ውሃ አንጠጣም። ከግዛትህ እስክንወጣ ድረስም የንጉሡን አውራ ጐዳና አንለቅም።”

23. ሴዎን ግን እስራኤል በግዛቱ ውስጥ እንዲያልፍ አልፈቀደም፤ ሰራዊቱን በሙሉ አሰባስቦ እስራኤልን ለመውጋት ወደ ምድረ በዳው ወጣ፤ ያሀጽ እንደ ደረሰም ከእስራኤል ጋር ጦርነት ገጠመ።

24. እስራኤል ግን በሰይፍ መታው፤ ከአርኖን እስከ ያቦቅ ድረስ ያለውንም ምድሩን ወሰደበት፤ ይሁን እንጂ የአሞናውያን ወሰን የተመሸገ ስለ ነበር ከያቦቅ አላለፈም።

25. እስራኤልም ሐሴቦንና በአካባቢዋ ያሉትን መንደሮች ጨምሮ የአሞራውያንን ከተሞች በሙሉ በመያዝ እዚያው ተቀመጠ።

26. ሐሴቦን የቀድሞውን የሞዓብን ንጉሥ ወግቶ እስከ አርኖን ድረስ ያለውን ምድሩን የወሰደበት የአሞራውያን ንጉሥ የሴዎን ከተማ ነበረች።

27. እንግዲህ ባለቅኔዎች እንደዚህ ያሉት ለዚህ ነው፤“ወደ ሐሴቦን ኑ፣ እንደ ገና ትገንባ፤የሴዎንም ከተማ ተመልሳ ትሠራ፤

28. “እሳት ከሐሴቦን ወጣ፤ነበልባልም ከሴዎን ከተማ ተንቦገቦገ፤የሞዓብን ዔር፣በአርኖን ከፍታዎች የሚኖሩትንም በላ።

29. ሞዓብ ሆይ፤ ወዮልህ!የከሞስ ሕዝብ ሆይ፤ ተደመሰስህ!ወንዶች ልጆቹን ለሽሽት፣ሴቶች ልጆቹን ለምርኮ፣ለአሞራውያን ንጉሥ ለሴዎን አሳልፎ ሰጥቶአል።

30. “እኛ ግን ገለበጥናቸው፤ሐሴቦን እስከ ዴቦን ድረስ ተደመሰሰች፤እስከ ኖፋ ድረስ ያሉትን፣እስከ ሜድባ የተዘረጉትን እንዳሉ አፈራርሰናቸዋል።”

31. ስለዚህም እስራኤል በአሞራውያን ምድር ተቀመጠ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘኁልቍ 21