ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘኁልቍ 21:14-26 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

14. እንግዲህ በእግዚአብሔር (ያህዌ) የጦርነት መጽሐፍ እንዲህ ተብሎ የተጻፈው በዚሁ የተነሣ ነው፤“ … በሱፋ ውስጥ የሚገኘው ዋሄብአርኖንና

15. ወደ ዔር የሚወስዱትበሞዓብ ድንበርም የሚገኙትየሸለቆች ተረተሮች።”

16. ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ለሙሴ፣ “ሰዎቹን በአንድነት ሰብስባቸውና ውሃ እሰጣቸዋለሁ” ወዳለበት ብኤር ወደተባለው የውሃ ጒድጓድ ጒዞአቸውን ቀጠሉ።

17. ከዚያም እስራኤል ይህን መዝሙር ዘመረ፤“አንተ ምንጭ ሆይ ፍለቅ!እናንተም ዘምሩለት፤

18. ልዑላን ለቈፈሩት፣የሕዝብ አለቆች በበትረ መንግሥታቸውና በበትሮቻቸው ላጐደጐዱት፣የውሃ ጒድጓድ ዘምሩለት።”ከዚህ በኋላ ከምድረ በዳው ወደ መቴና ሄዱ፤

19. ከመቴና ወደ ነሃሊኤል፣ ከነሃሊኤልም ወደ ባሞት፣

20. ከባሞትም ፈስጋ ላይ ሆኖ ምድረ በዳው ቊልቊል ወደሚታይበት በሞዓብ ወደሚገኘው ሸለቆ ተጓዙ።

21. እስራኤል ወደ አሞራውያን ንጉሥ ወደ ሴዎን እንዲህ የሚሉ መልእክተኞች ላከ፤

22. “በአገርህ አልፈን እንድንሄድ ፍቀድልን፤ ወደ የትኛውም ዕርሻ ሆነ የወይን አትክልት አንገባም፤ ወይም ከየትኛውም ጒድጓድ ውሃ አንጠጣም። ከግዛትህ እስክንወጣ ድረስም የንጉሡን አውራ ጐዳና አንለቅም።”

23. ሴዎን ግን እስራኤል በግዛቱ ውስጥ እንዲያልፍ አልፈቀደም፤ ሰራዊቱን በሙሉ አሰባስቦ እስራኤልን ለመውጋት ወደ ምድረ በዳው ወጣ፤ ያሀጽ እንደ ደረሰም ከእስራኤል ጋር ጦርነት ገጠመ።

24. እስራኤል ግን በሰይፍ መታው፤ ከአርኖን እስከ ያቦቅ ድረስ ያለውንም ምድሩን ወሰደበት፤ ይሁን እንጂ የአሞናውያን ወሰን የተመሸገ ስለ ነበር ከያቦቅ አላለፈም።

25. እስራኤልም ሐሴቦንና በአካባቢዋ ያሉትን መንደሮች ጨምሮ የአሞራውያንን ከተሞች በሙሉ በመያዝ እዚያው ተቀመጠ።

26. ሐሴቦን የቀድሞውን የሞዓብን ንጉሥ ወግቶ እስከ አርኖን ድረስ ያለውን ምድሩን የወሰደበት የአሞራውያን ንጉሥ የሴዎን ከተማ ነበረች።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘኁልቍ 21