ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘኁልቍ 2:27-31 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

27. “የአሴር ነገድ ከእነዚህ ቀጥሎ ይሰፍራል፤ የአሴር ሕዝብ አለቃ የኤክራን ልጅ ፋግኤል ሲሆን፣

28. የሰራዊቱም ብዛት አርባ አንድ ሺህ አምስት መቶ ነው።

29. ከዚያም የንፍታሌም ነገድ ይቀጥላል፤ የንፍታሌም ሕዝብ አለቃ የዔናን ልጅ አኪሬ ሲሆን፣

30. የሰራዊቱም ብዛት አምሳ ሦስት ሺህ አራት መቶ ነው።

31. “በየሰራዊታቸው ሆነው ከዳን ምድብ የተመዘገቡት ወንዶች ሁሉ አንድ መቶ አምሳ ሰባት ሺህ ስድስት መቶ ናቸው፤ እነርሱም በዐርማቸው ሥር በመጨረሻ ይመጣሉ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘኁልቍ 2